Faith Statement of EFGBC
1. ስድሳ ስድቱን የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻህፍት የያዘውን መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር እስትንፋሳ ቃል፣ ምንም ስህተት የማይገኝበት ፣ እምነትን እና
ተግባርን በሚመለከት ሁሉ የመጨረሻው ሥልጣን ያለው ፣ህያው እና ዛሬም የሚሰራ ፣ እንደ ሆነ እናምናለን፡፡
2. በእግዚአብሔር አብ፣ በእግዚአብሔር ወልድ፣ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፣ አንድ አምላክ ፣እናምናለን፡፡
3. በመፍጠር ስራ፣ ፍጥረትን በመጠበቅ ፣ በመገለጥ ፣በመዋጀት እና በመጨረሻው ፍርድ የእግዚአብሔርን ፍፁም ሥልጣን እና የበላይነት እናምናለን፡፡ 4. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአብ የተላከ መሆኑን ፣ በመንፈስ ቅዱስ መፀነሱን ፣ ከድንግል ማርያም መወለዱን ፣ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ መሆኑን ፣
ለሰው ልጃች ቤዛ ሆኖ በመስቀል ላይ መሞቱን ፣ መቀበሩን፣ በሶስተኛው ቀን በአካል ከሙታን መነሳቱን፣ ወደ አብ ማረጉን እና አሁንም በአብ ቀኝ ሆኖ ስለ እኛ እንደሚማልድ ፣ ደግሞም በህያዋንና በሙታን ላይ ሊፈርድ በክብርና በግርማ እንደሚመለስ እናምናለን፡፡
5. መንፈስ ቅዱስ የመለኮት ባሕርያት ሁሉ ያሉት ፍጹም አምላክ እንደሆነ እና አምልኮ እና ስግደት እንድሚገባው እናምናለን፡፡ 6. ሰው በእግዚአብሔር አምሳል መፈጠሩን ፣ በኃጥያት መውደቁን እና በዚህም ምክንያት የእግዚአብሔር ቁጣና ፍርድ ያለበት በደለኛ መሆኑን እናምናለን፡፡
7. ሰው ከኃጢአት ዕዳ ፣ ኃይልና ቅጣት ፣ ሊድን የሚችለው ኃጥያት የለለበት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ምትክ ሆኖ በፈጸመው የቤዛነት ስራ ብቻ በመሆኑ ኃጥያተኛ በእግዚአብሔር ፀጋ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ብቻ እንደሚጽድቅ እናምናል፡፡
8. ኃጥያተኛ በኃጥያቱ ተፀጽቶ ንሰሐ እንዲገባ ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ዳግመኛ በመወለድ አዲስ ፍጥረት እንዲሆን መንፈስ ቅዱስ በህይወቱ እንሚሰራ እናምናልን፡፡
9. መንፈስ ቅዱስ በአማኝ ህይወት ውስጥ እንደሚኖር ፣ አማኙ በመንፈስ ቅዱስ ሲጠመቅ ኃይልን እንደሚቀበልና በልሳን እንደምናገር በየጊዜውም በመንፈስ ቅዱስ እንደሚሞላ እናምናለን፡፡
10. መንፈስ ቅዱስ ዛሬም ቤተ ክርስቲያንን ለማነጽ ለአማኞች ልዩ ልዩ የጸጋ ስጦታዎችን በማካፈል፣ድውዮችን በመፈወስ ፣ አጋንትን በማውጣትና ፣እና ተዐምራትን በማድረግ እንመድሰራ እናምናለን፡፡
11. ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ የተሰጣትን የታላቁን ተልዕኮ አደራ በመወጣት ወንጌልን ለሰዎች ሁሉ እንድትሰብክ እና አማኞች ደቀ መዛሙርት በማድረግ ለክርስቶስ አካል መታነጽ አስፈላጊውን ሁሉ መፈጸም እንደምትችል መንፈስ ቅዱስም ሐዋርያትን፣ ነቢያትን፣ ወንጌል ሰባኪዎችን ፣እረኞችን እና አስተማሪዎችን እንዲሁም ሌሎች የአገልግሎት ስጦታዎችን እንደሚሰጥ እናምናለን፡፡
12. ከእግዚአብሔር መንፈስ ዳግም የተወለዱ ሁሉ በሚገኙባት፣ የክርስቶስ አካል በሆነች፣ በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን፡፡ 13. ጌታችን እና መድኅንታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ባዘዘው መሰረት ፣ዳግም የተወለደ አማኝ ከክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ ጋር መተባበሩን እንዲሁም ለኃጥያት መሞቱን እና ለጽድቅ መነሳቱን ለመግለጽ በአብ፣ በወልድ፣ እና በመንፈስ ቅዱስ ስም በውኃ ውስጥ በመጥለቅ እንዲጠመቅ እንዲሁም ጌታ ዳግም እስኪመጣ ሞቱን ለመናገርና ፣ ከጌታ እና ለአማኞች ጋር ያለውን ኅብረት
ለመግለጽ የጌታ እራት እንደሚካፈል እናምናለን፡፡
14. በሙታን ትንሳኤ፣ በኃጥያተኞች ላይ በሚደርሰው የዘላለም ፍርድና አማኞች በሚቀበሉት የዘላለም ህይወት እናምናለን፡፡
1. We believe that the Bible, containing the sixty-six books of the Old and New Testaments, is the inspired Word of God, inerrant, infallible, and the final authority for all matters of faith and practice, living and active today.
2. We believe in God the Father, God the Son, and God the Holy Spirit, one God.
3. We believe in the absolute authority and sovereignty of God in creation, in the preservation of creation, in revelation, in redemption, and in the final judgment. 4. We believe that our Lord Jesus Christ was sent from the Father, conceived by the Holy Spirit, born of the Virgin Mary, fully man and fully God,
that he died on the cross as a ransom for mankind, was buried, rose bodily from the dead on the third day, ascended to the Father, and is now at the right hand of the Father, interceding for us, and will return in glory and majesty to judge the living and the dead.
5. We believe that the Holy Spirit is fully God, possessing all the attributes of the Godhead, and is worthy of worship and adoration. 6. We believe that man was created in the image of God, fell into sin, and is therefore a sinner under the wrath and judgment of God.
7. We believe that man can be saved from the debt, power, and punishment of sin only through the work of the sinless Son of God, Jesus Christ, who was made man’s substitute, and that the sinner is justified by the grace of God through faith in Jesus Christ.
8. We believe that the Holy Spirit works in the life of the sinner to repent of his sins, to believe in Jesus Christ, and to become a new creation by faith in Jesus Christ.
9. We believe that the Holy Spirit lives in the life of the believer, that the believer receives power when he is baptized in the Holy Spirit, and that he speaks in tongues and is filled with the Holy Spirit from time to time.
10. We believe that the Holy Spirit continues to work in the church today to build up believers by imparting various gifts of grace, healing the sick, casting out demons, and performing miracles.
11. We believe that the Church, in fulfilling the great commission given to her by Christ, is empowered by the Holy Spirit to preach the gospel to all people and to make disciples of believers, and to do all that is necessary for the building up of the body of Christ.
12. We believe in one holy church, the body of Christ, in which all who are born again of the Spirit of God are gathered. 13. We believe that, according to the command of our Lord and Savior Jesus Christ, a born-again believer is baptized by immersion in water in the name of the Father, the Son, and the Holy Spirit, in symbol of his death and resurrection from sin and his resurrection to righteousness, and that he partakes of the Lord’s Supper to proclaim his death and to express his fellowship with the Lord and the believers until the Lord’s return.
14. We believe in the resurrection of the dead, the eternal judgment of sinners, and eternal life for believers.